Jul 31, 2014

“ማንዴላ” በኤፍሬም ስዩም ተሰማ



“ማንዴላ”


ነጻነት ነው የወጣኸው?
ነጻነት ነው የወጣችው?
ለነጻነት ነው ለነጻነታችሁ?
ለግል ማንነትህ ወይስ ላ’ገራችሁ…?
ያገርህ ላይ ጥቁሮች ዛሬን ይጠግባሉ?
ባገራቸው መሬት እነርሱ ያርሳሉ?
ወይስ የነጭን ዘር ቃርሚያ ይለቅማሉ…?!

`ስድስት ወራት በከለለህ
ባገሬ አፈር ልጠይቅህ
እውነት ነው ማንዴላ? የውነት ነጻ ሰው ነህ?`

ነጻም ነኝ ካልክ ማን አሳዶ ማን መለሰህ?
ማንስ አስሮ ማን አስፈታህ? ማን አቁስሎ  ማን ጠገነህ?
‹‹ኖቤል›› ማን ሸለመህ? ነጻነት ማን ነሳህ?

`ስድስት ወራት በከለለህ
ባገሬ አፈር ልጠይቅህ…
እውነት ነው ማንዴላ የውነት ነጻ ሰው ነህ?`
ያገርህ ላይ ጥቁሮች ዛሬን ይጠግባሉ?
ባገራቸው መሬት እነርሱ ያርሳሉ?
ወይስ የነጭን ዘር ቃርሚያ ይለቅማሉ?

`ስድስት ወራት በከለለህ
ባገሬ አፈር ልጠይቅህ
እውነት ነው ማንዴላ የውነት ነጻ ሰው ነህ?`
*****
ነጻ ነኝ ካልክ በማን በሬ ነው
የማን ሰርዶ የሚጋጠው?
ማንስ ጫንቃ ላይ ነው ነጫጭ ውሻ የታሰረው?
እኮ እንዴት?
እድሜን አስረጅቶ ደረስኩልህ ማለት¡
ነጻነትን ነፍጎ ‹‹ኖቤል›› ሸላሚነት
እኮ እንዴት….?

ይልቅስ ልንገርህ ተረት ነው ነጻነት
ደሮን ሲደልሏት በመጫኛ ጣሏት!
አርዝመው ቢያስሯት የፈቷት መሰላት..
ለዚህም ሁሉ ነጻነትን ነፍጎ ለነጻነት ታጋይ ‹‹የኖቤል›› ሽልማት
ማታለል ይመስላል ምጸት እና ኩሸት…!

ስድስት ወራት በከለለህ
ባገሬ አፈር ልጠይቅህ
እውነት ነው ማንዴላ የውነት ነጻ ሰው ነህ…?
ያገርህ ላይ ጥቁሮች ዛሬን ይጠግባሉ?
ባገራቸው መሬት እነርሱ ያርሳሉ?
ወይስ የነጭን ዘር ቃርሚያ ይለቅማሉ?
“ስድስት ወራት በከለለህ
በመንደርህ በኩልፌ አፈር ልጠይቅህ
አውነት ነው ማንዴላ የውነት ነጻ ሰው ነህ….?”
በኤፍሬም ስዩም ተሰማ
‹‹ሙዚ-ቃል›› የግጥም ሸክላ

Jul 29, 2014

ቁልቢ



ቁልቢ


ከአራቱም መዓዘናት የሚመጡ ሰዎችን የምታስተናግደው ቁልቢ  ለድሬዳዋመ ሆነ ለሐረር ቅርብ ስትሆን፤ በዓመት ውስጥ በተለይ ታህሳስ እና ሐምሌ ወር ላይ ከፍተኛ የሆነ ምዕመንን ታስተናግዳለች፡፡
የቁልቢ ገብርኤል ሲባል ሁላችንም እንሰማለን፡፡ ታሪኩን በአጭሩ ለመጥቀስ ስንሞክር፡-
 በዮዲት ዘመን ከአክሱም ጽዮን ጽላተ ሙሴ ጋር በደባልነት ይኖር የነበረውን የቅዱስ ገብርኤልን ጽላት እና ንዋዬ ቅዱሳቱን ይዘው ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ጉዙ ቀጥለው፤ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በዝዋይ ሀይቅ ውስጥ ደብረ ጽዮን ማርያም ተብላ ከምትጠራ ደሴት እንደተቀመጡ መዛግብት ያስረዳሉ፡፡
በዚያን ጊዜ የ5 ዓመት ንጉስ እንደነበር የሚነገረው አንደሳ ውዱም፤ ዮዲት ከ40 ዓመታት በኋላ ከዙፋን ስትወርድ በሸዋ ተሸሽጎ የነበረው አንበሳ ውዱም ተመልሶ አክሱም ላይ ነገሰ፡፡
በዚህም ጊዜ በዮዲት የተቃጠለውን የአክሱም ጽዮን ቤተክርስትያን አሳድሶ ጽላቱን ሲያኖር የቅዱስ ገብርኤል ጽላት (ታቦት) እንዳልተመለሰ ተነገረው፡፡
ይሕም ለምን ሆነ ሲባል ካህናቱ ከሁሉም ንዋዬ ቅዱሳት እና ታቦተ ጽዮን(ጽላተ ሙሴን) ጨምረው ለመውሰድ ሲሞክሩ የቅዱስ ገብርኤል ታቦት ግን ለመነሳት ‹‹እምቢ አለ››፡፡
ንጉሱም አዘኑ፡፡ በዚህ ወቅት ኤርትራ ውስጥ ከሚገኝ አባ አጽቀ ሌዊ የተባሉ ባህታዊ መጥተው ታቦቱን እንዲያመጡት ፈቃድ ጠየቁ፡፡
በማህተም የተደገፈ የይለፍ ደብዳቤ እና ስንቅ ይዘው ዝዋይ ደብረ ጽዮን ማርያም ደረሱ፡፡ /እንግዲህ ከዛሬ አንድ ሺህ ዓመት በላይ ኤርትራ፣ ደቡቡ የኢትዮያ ክፍል ይገናኙ እንደነበር ማሰብም ያስደስታል/
እቦታው ደርሰው ታቦቱንም ይዘው ሲወጡ አንድ ሰው ከፊት ቆሞ “ወዴት ትሄዳለህ?” ብሎ ጠየቃቸው፡፡ ወደ ሰሜን እንደሆነ መለሱላቸው፡፡ ወደ ሰሜን መሄድ እንደሌለበት እና ወደ ምስራቅ መሄድ እንዳለበት ይነገራቸዋል፡፡
የንጉስ ትዕዛዝ እንደሆነና ወደ ምስራቅ መሄድ እንደማይችሉ ነገር ግን ወደ ሰሜን መሄድ እንዳለባቸው ተናገሩ፡፡ በዚህ ክርክር መሃል ተናጋሪው ሰው ወደ ብርሃን ተለወጠ፤ ተናጋሪውም የጽላቱ ባለቤት ገብርኤል መሆኑ ተነገራቸው፡፡ ተከተለኝ በሚል ትዕዛዝ ጉዟውን ቀጠሉ…፡፡
አባ አፅቀ ሌዊም በመልዐኩ ቅዱስ ገብርኤል ተመሪነት ወደ ተቀደስ ተራራ ታህሳስ 19 ቀን ሀረርጌ ጠቅላይ ግዛት እንደደረሱ ተዓምሩ ላይ ተጠቅሷል፡
ባህታዊውም ቃልኪዳኑን ከመልዐኩ ተቀብለው በጾም በጸሎት ከኖሩ በኋላ ታሪኩን በድንጋይ ላይ ጽፈው በማኖር፤ ስውር ሆኖ እንዲኖር በማድረግ  ህልፈተ ሕይታቸውን ተቀበሉ፡፡
ከዚህም በኋላ ለብዙ ዓመታት ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምስራቅ 150 ኪ.ሜ በቡልጋ አምባ በአጋዥጌ ካህናተ ሰማይ ቤተክርስትያን ውስጥ በደባልነት ይኖር ነበር፡፡
አጼ ምኒልክ በ1882 ሀረርን ሲጠቀልሉ ራስ መኮንን ከሾሙ በኋላ፤ ራስ መኮንን ሀረርን መናገሻ ቢያደርጉም ቁልቢንም በነበራት የቅዝቃዜ አየር ጠባይ እንደ ሁለተኛ ከተማቸው እንደመረጡ ይነገራል፡፡
ራስ መኮንንም ይሕንን ቦታ ከባህታዊያን ጋር በመነጋገር የነበረውን ታሪክ በመረዳት ታቦቱ መጥቶ እንዲቀመጥ አድርገዋል፡፡ ቦታውንም መጠነኛ መጠለያ በማዘጋጀት ካስቀመጡ በኋላ ስዕለት እንደተሳሉም የሚነገር ሲሆን፤ አካባቢን ሰላም ካደረክልኝ ህንጻ እንደሚያሰሩ ተሳሉ፤ …ይሕም ሆነ፡፡
አድዋ ሲዘምቱ እዚህ ቤተ-ክርስትያን ጸልየው፣ ቆርበው እና ተስለው እንደሄዱም ይነገራል፡፡ በብዛት እንደ አሁኑ ሰው የማይጎበኘው የበነረበት ወቅት እንዳለ ቢታወቅም፤ አጼ ኃይለ ሥላሴ በ1954 ዓ.ምህረት የህንጻው መሰረት ድንጋይ አኖረው፤ በ1957 ዓ.ምህረት ታኅሣሥ 19 ቀን ተመረቀ፡፡/ በ423 ሺህ ብር እነደሆነም ተጠቅሷል/፡፡.. አጠቃላይ ታሪኩን ለማግኘት መዛግብትን ማጋላበጥ እንሚያስፈልግ እየጠቀስኩ መ/ር ኃይለ መስቀል ፋንታሁን ያዘጋጀውን ባለ 40 ገጽ ጥራዝ ለዚህ ጽሑፍ ዋቢ አድርጌ የተጠቀምኩ መሆኑንም በማጣቀስ ለአዘጋጁ ላቅ ያለ ምስጋዬን አቀርባለሁ፡፡

በቁልቢ ገብርኤል ምን እንታዘባለን…?
ህንጻ ቤተክርስትያኑ ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር መተዳደሪያ ደንቡንም አብሮ መመልከት ይቻላል፡፡ ከክርስትና ትምህርት መስፋፋት ጥቅም ባሻገር ሌሎች እሴቶችን ይዞ እንደተመሰረተም መመልከት ይቻላል፡፡
በመኪና ፓርክ በኩል ከፍተኛ የሆነ ምስቅልቅል/ ብዛት ስላለበት/ የሚታየውን ችግር ለመፍታት ዘመናዊ የሆነ አሰራር እንደሚያስፈልግ ለመገንዘብ ይቻላል/
አካባቢውን ማደራጀት፣ ከተማዋን ማሳደግ እና በተለይ ከከተማዋ ወደ ደብሩ የሚወስደውን መንገድ ‹‹በአስፓልት›› አሊያም ‹‹በኮልብ ስቶን›› ማልበስ ግድ የሚባልበት ወቅት ላይ ነን፡፡ ይሕም ደብሩ ከሚየገኘው የስዕለት ገቢ እና በየጊዜው የሚሄደውን ምዕመን ለዚህ አገልግሎት የሚል የገንዘብ ማሰባሰብ መርሃ ግብር አዘጋጅቶ ማሳካት የሚቻል ሲሆን፤ መንግስትም የበኩሉን ድርሻ መወጣት አለበት፡፡
ከከተማዋ እስከ ደብሩ ያለው ስፍራ የረብሻ እና የምስቅልቅል ሂደት እንደሆነ መመልከት ይቻላል፡፡ ቤተክርስትያናችን የንግድ መገበያያ መንገድ አድርጎ መውሰድ እና ይሕንንም ስርዓት ማስቀጠል የክርስቶስን ጅራፍ መቀበል ነው፡፡ ‹‹የሞንታርቦች›› እና የረብሻ ድምጽ የአርምሞ እና የጸጥታ እንዲሁም የመረጋጋት መንፈስን አይፈጥርም፡፡ / ደብሩ ቅጥር ግቢ ውስጥ ስንገባ ግን የተሻለ መረጋጋት እና ጸሎት ለማድረስ ሚያስችል ድባብ ነበረው፡፡
የስርቆት ነገር አያድርስ ነው፡፡ የቦታውን ኃያልነት እና ቅዱስነት በከፍተኛ ሁኔታ ያሳጣዋል፡፡ ለስርቆት ብቻ የሚመጡ አረመኔዎች እንዳሉም ይነገራል፡፡ / ስራውን አምላክ ካላገዘን ቀላል ነገር አይደለም/ ፖሊሶች ጳጳሱን ከሚጠብቁበት ጥንካሬ አንጻር ለምዕመኑም በተመጣጣኝ ሁኔታ ሊያስቡበትት ይገባል፡፡
መብላት፣ መጠጣት፣ መስከር ከኃይማኖት ስርዓት አንጻር የማይዛመዱ ናቸው፡፡ ቤተክርትያን በየሓይማኖት ስርዓቶች ይሕንን አይነት ነገር በማስተዋል በከፍተኛ ሁኔታ ከሚጠበቀው በላይ እየተስፋፋ በመሄዱ ማውገዝ አለባት፡፡ ነጋዴው ይሕንን ነገር ባይፈልግም ቦታው ላይ አልኮል መጠጦችን እና ከሐይማኖት ስርዓት ውጭ የሆነውን ነገር ሁሉ መቆጣጠር መቻል አለብን፡፡  የቢራ ፋብሪካ ማስታወቂያዎች “እንኳን ለቁልቢ ገብርኤል በዓል አደረስዎ” ብለው ሰፋፊ መጋረጃዎችቸን ሰቅለው ተመልክተናል፡፡ ….እኛንም ጋርደውብናል፡፡
ሐይማኖታችንን መጠበቅ ያለብን እኛ ነን፡፡ ይሕን ነገር ልንቃወም ይገባል፡፡ እርግጥ  ደብሩ ቅጥር ግቢ በተቃረብን ቁጥር እና ቅጥር ግቢው ውስጥ ይህ አይነት ችግር አለ ባንልም…አነስተኛዋን የቁልቢ ከተማ መቆጣጠር እና በተለይ በዓሉን በምናከብርበት ጊዜ ሃይማኖታዊ ስርዓቱ ተጠብቆ በረከቱን ተካፍለን ብንመለስ አማራጭ የማይቀርብለት መንገድ ነው፡፡
ይሕ ሁሉ ህዝብ ምን ይሳላል…?
መቼስ ስዕለት በልብ ለእግዚአብሔር ብቻ የሚነገር የሕይት ፍላጎት ነው፡፡ ጣልቃ አንገባም፡፡ ሁሉም ሰው ግን ለራሱ ብቻ ስዕለቱን ተናግሮ፤ ከሚመለስ በሕብረት ብንጸልይ እና በአገራችን ስርዓት ያለበትን፣ እውቀት የሚስፋፋበትን መረዳዳት የሚስተዋልበትን የማስተዋልና እና የጥበብን ስብዕና እንዲያላብሰን ብንመኝ ሊሻል እንደሚችል በግሌ ሃሳቤን እሰነዝራለሁ፡፡  ሰላም ያገናኘን!! ታኅሳስ 19/ 2006 ሀረር

Jul 18, 2014

ቅኝት ባሕርዳር- ዋጋ ካስከፈሉኝ መጽሐፍት ጋር

24 ሰዓታት ‹‹ከአብርሃ ድስታ›› ጋር ¡ ¡ ¡
የምታነቧቸውን መጽሐፍት በእርግጥ ልብ ብለዋቸኋቸው ያውቃሉ? ዋጋ የሚያስከፍሉት መጽፍሐት ለምሳሌ፡-
‹‹እኛ እና አብዮቱ››፤ ‹‹አቤቶ ኢያሱ አነሳስና አወዳደቅ››፤ ‹‹ኃይለ ማርያምን ፍለጋ››፤ ‹‹የትግራይ ህዝቦች ወያኔዎቹና ሽፍቶች››፤‹‹ዶ/ር አሸብር››፤ ‹‹ኡመተ ፈናን ኡመተ ቀሽቲ ድሬዳዋ››፤ ‹‹ያ ትውልድ››፤ ‹‹ከደርግ ማህደር››፤ ‹‹የአሲምባ ፍቅር››፤ ‹‹የካድሬው ማስታወሻ››፤ ‹‹ህዝብና ነጻነት››፤ ‹‹101 የሰላማዊ ትግል መንገዶች›› ፤ ‹‹ያልተሄደበት መንገድ››……… ዋጋ ያስከፈሉኝ መጽሐፍት…..¡¡¡¡¡¡¡¡¡¡¡

‹‹ቅኝት ባሕርዳር- ዋጋ ካስከፈሉኝ መጽሐፍት ጋር¡¡¡¡¡¡››
‹‹‹‹‹‹‹ተስፋ በላይነህ›››››››
……
‹‹አባዱላው›› ወደ ባሕር ዳር የያዛቸውን ሰዎች ይዞ፤ አንድ የቀረው እያለ ሲጣራ፤ አንደኛው እኔ ነበርኩ፡፡ ተያይዘን ጉዞ ወደ ጣና ዳር፡፡ የክረምቱን ዝናብ እያቆራረጥን፣ አረንጓዴዋን ኢትዮጵያ እያማተርን፤ የለመለመውን መስክ እየሸኘን የጣና ዳርን ከተማ ጸሐይ ስትሸሻት- እኛ ስንደርስ እኩል ተገጣጠምን…! ‹‹ተገጣጠሙ›› የሚለው ሙዚቃ በረዥሙ ይሰማም ነበር፡፡
በጉዞ ላይ ባለ ‹‹አምስት›› ወይንም ባለ ‹‹አራት ኮከብ›› ሆቴሎችን መዳሰስ አይመቸኝም፡፡ ለምን አይመቸኝም?  ራሳችሁ ናችሁ የምታውቁት፡፡ ለኔ ግን አይመቹኝም…..-፡፡
ይልቁንስ “couch surfing” የሚባል ድህረ ገጽ አለ፡፡ መንገደኞች ዓለምን ሲዞሩ የሚገለገሉበት ነው፡፡ ምናልባትም ኢትዮጵያዊ መንገደኞች/ tourists/ አባል የሚሆኑበት እና አንድ ሰው ወደ አንድ አገር/ከተማ መንገድ ሲያስብ አስቀድሞ በዛ አገር ውስጥ አሊያም ከተማ የ “couch surfing” አባል የሆነን ግለሰብ መልዕክት ይልክለታል፡፡
ለምሳሌ እኔ፡-
ወደ ባህር ዳር ጉዞ ሳቀና አስቀድሜ ባህር ዳር ለሚኖር አንድ የ couch surfing አባል መልዕክት መላክ ይጠበቅብኛል፡፡
“ታዲያስ አበበ- እኔ ሐምሌ 11 እንደ ኢትዮጵያን አቆጣጠር ወደ ባሕር ዳር እመጣለሁ፡፡ የምቆየው ሁለት ቀናት ብቻ ሲሆን አንተ ቤት ላርፍ ዘንድ በእንግድነት ብትቀበለኝ ምን ይመስልሃል? የማይመችህ ከሆነ ሌላ አማራጭ ልጠቀም፡፡ እጅግ አድርጌ አመሰግንሃለሁ፡፡ ያንተው፡፡” የሚል፡፡
ይህንን ያነነበበ ሰውም እንደ ፈቃደኝነቱ እና እንደ ጊዜው ሁኔታ እሺታውን አሊያም የማይመቸው መሆኑን ይገልጻል፡፡ ሁሉም በኢንተርኔት ነው ግንኙነቱ፡፡ አንተዋወቅም….-፡፡
ለዛሬ አልተሳካልኝም፡፡ የዛሬው የ “couch surfing” አባል ሌሎች እንግዶችን ስለሚያስተናግድ እንደማይመቸው ‹‹በኢሜሌ› ደረሰኝ፡፡ ያለው አማራጭ ሌላ የ couch surfing አባል መፈለግ አሊያም ዘመድ ጋ መደወል፡፡ ‹‹ባለ አምስት ኮከብ›› ሆቴል ማፈላለግ ጠፍቶኝ እንዳይመስላችሁ፡፡…. አይደለም፡፡ ጭራሽ አ.ይ.መ.ቸ.ኝ…..ም!!! ሃሃሃሃሃ
ዘመድ ጋር ስደውል እሺታው በአንዴ ነበር የተገኘው፡፡
“የመሸበት እንግዳ ትቀበላላችሁ?” ከዘመናዊው ከውች ሰርፊንግ ባሕላዊው የእንግድነት ጥየቃ ተሳካ፡፡
“የመሸበት እንገዳ ትቀበላላችሁ?”
ዘመዴ እንዲህ መለሰች፡፡ “ተገኝቶን ነው…!!”
ባጃጅ ኩንትራት ወደ ‹‹አየር ሓይል›› ሰፈር፡፡ ቦታው ወደ ባሕር ዳር ኤርፖርት ወደ ሚወስደው መንገድ ስለሆነ አንድ ምስኪን የባጃጅ ሾፌር እንዲወስደኝ ጠይኩት፡፡ በነገራችን ላይ ባጃጅ ኩንትራት ስትጠይቁ ሾፌሩ የገጠር ሰው ከሆነ ታድላቹሃል፡፡
እዋራችሁ… የልብ የልቡን እያጫወታችሁ… ትጓጓላችሁ… አይሰለቻችሁም፡፡ መንገድ ላይ አቁሞም..
“አየህ ወደ ዘመድ ቤት ሲኬድ ባዶ እጅ አይገባም፡፡ በቆሎ.. ሙዝ አሊያም ብርቱካን ተይዞ ነው የሚኬደው!!” ብሎ የዘመድ ጥየቃ ደንቡን በግልጽ ያማክሮታል፡፡ እንዲህ ያለ የባጃጅ ሾፌር ከወዴት ይገኛል…?
እየመሸ ስለሆነ መንገድ ዳር ከሚገኝ ትልቅ ገበያ/ super market/ ጎራ ብዬ፤ ትንሽ ነገር  አንጠልጥዬ፤ ጎዟችን ቀጠልን፡፡ ወደ አየር ኃይል መንደር፡፡
ዋናውን የኤርፖርት መንገድ ሳንጨርስ፤ ወደ ቀኝ ‹‹ፒስታ›› መንገድ ታጥፈን ትንሽ እንደገባን፤ የአየር ኃይል መንደር የመጀመሪያው መግቢያ በር ላይ ቆሜ ስልክ ወደልኩ፡፡ ጸጥ ያለ በከፍተኛ ቁጥጥር የሚጠበቅ መንደር ነው፡፡ ጸጥታውን ወደድኩት….!
ዘመዶቼ መጡ፡፡
በር ላይ የመሸጉት የመከላከያ ልብስ የለበሱ ሶስት ወንዶች እና ሁለት ሴቶች ለፍተሻ ተባበሩን ተባለ፡፡
ጥሎብኝ የመከላከያ ሰዎችን እግባባቸዋለሁ፡፡ ሊፈትሱኝ ሲቀርቡ… ላፕቶፔን እንዲህ እቀልዳቸዋለሁ፡፡
“አይ ትንሽ ቢጤ ቦንብ ናት….¡” እላቸዋለሁ
ብዙዎቹ ይስቃሉ፡፡
መታወቂያ ተጠየኩ፡፡
አሳየሁ፡፡
በጀርባዬ ያዘልኩትን እንዳወርድ ተጠየኩ፡፡
አሳየሁ፡፡
ላፕቶፕ ነው…፡፡ /ቦንብ ነው ማለት አይቻልም፡፡/ ሁልጊዜ ሲቀለድ አይኖርም!!!! ጠንቀቅ ነው አንዳንዴ፡፡
ቀጥሎም በእጄ የያዝኩት ጓዝ እንዲፈተሽ ተጠየኩ፡፡
ተከፈተ፡፡
መጽሐፍ እንደበዛ ተመለከቱ፡፡
“አንባቢ ነህ ባክህi?” አለኝ፡፡
“ያው ምን ስራ አለ ብለህ ነው…?” አልኩት፡፡
የመጽሐፍቶቹን አርዕስት መመልከት ቀጠለ፡፡
‹‹እኛ እና አብዮቱ››
‹‹አቤቶ ኢያሱ አነሳስና አወዳደቅ››
‹‹ኃይለ ማርያምን ፍለጋ››
‹‹የትግራይ ህዝቦች ወያኔዎቹና ሽፍቶች››
‹‹ዶ/ር አሸብር›› ደሞ እቺ ምንድናት? እያለ ማንበብ ቀጠለ፡፡
‹‹ኡመተ ፈናን ኡመተ ቀሽቲ ድሬዳዋ››፡፡ ምን ማለት ነው? ብሎ ጠየቀኝ ወደ ርዕሱ እየጠቆመ… “አይ …” ብዬ ሳልጨርስ ወደሌላው ቀጠለ፡፡
‹‹ያ ትውልድ››
‹‹ከደርግ ማህደር››
‹‹የአሲምባ ፍቅር››
‹‹የካድሬው ማስታወሻ››
‹‹ህዝብና ነጻነት››
‹‹101 የሰላማዊ ትግል መንገዶች›› ብሎ ካነበበ በኋላ በታላቅ ጥርጣሬ አይን ተመለከተኝ/ ገላመጠኝ/ ብል አልተሳሳትኩም፡፡.. ኩም ብዬ ቀረሁ…
‹‹ያልተሄደበት መንገድ›› ላይ ሲደርስ ሙሉ በሙሉ አቆመ፡፡
“ወደ የት ነው የምትሄደው አንተ?” ብሎ ጠየቀኝ፡፡
“አይ…” እንዳልኩ አሁንም ሊያስጨርሰኝ አልቻለም፡፡
ወዲያዉኑ ያዘውን ሬድዮ/ ወኪቶኪ/ ከጀርባው መዥለጥ  አድርጎ፡፡ የኮድ ቁር ነካ፡፡
“ጥቁር በሬ” ብሎ ሲናገር ብቻ ሰምቸዋለሁ፡፡
ከዛ ወደ አራት የሚደርሱ ጥቋቁር ቪ ስምንት/V-8/ ‹‹ኮብራ›› መኪናዎች ከጀርባዬ ከበቡኝ፡፡ አራቱም በእኩል ፍጥነት ተከፈቱ፡፡
የያዝኩትን ላፕቶፕ እና መጽሐፍቶቹ እንዱሁም እኔ ለምርመራ እንደምፈለግ ነግረውኝ ወደ መሃከለኛዋ ‹‹ኮብራ›› መኪና እንደገባ ጠየቁኝ፡፡……. ከብዙ መንገድ በኋላ….
የት እንዳለሁ ኣላውቅም፡፡… ጭለማ ክፍል ውስጥ ነኝ፡፡
የአንድ ሰው ድምጽ ሰማሁ፡፡
ስሙን ሲነግረኝ ለማመን አልቻልኩም፡፡ አብርሃ ደ..ስ……ታ!!!!!!!????? እባላለሁ የሚል ድመጽ ሰማሁ…..
ይቀጥላል፡፡
ቀጣዩን ክፍል ለማንበብ ይህንን ጠቅ ያድርጉ…
…….
ቀን ቀን በብስክሌት ማታ በ ‹‹ኮብራ›› 

….ወደ አየር ኃይል መንደር የወሰደኝ የባጃጅ ሾፌር ዋጋ ጠየኩት…
“ደስ ያለህን ስጠኝ” ብሎ ፈገግ አሳኘኝ፡፡
20 ብር አልኩት፡፡ እሺ ብሎ ልቤን ነካው…
“50 ብር መስጠት ነበር….” ብዬ አሰብኩና 30 ብር ሰጠሁት፡፡ በጣም ተደሰተ…. ይህን ዐይነት አባባል ያገኘሁት ከኮሜዲያን ልጅ ያሬድ ነበር፡፡ ልጅ ያሬድ ማታውን  ዮሴፍ በቤት ውስጥ ትዕይንት///‹‹በጆሲ ኢን ዘሐውስ ሾ››/// ሲያዝናናን ነበርና….!
ወደ መጀመሪያው መግቢያ በር ስደርስ፤ ስልክ ደወልኩ፡፡ ዘመዴ መጣች፡፡ ከባለቤቷ ጋር፡፡
መታወቂያ ተጠየኩ፡፡
አሳየሁ፡፡ ስሜ ተመዘገበ፡፡ ያለምንም ፍተሻ እንድገባ ተጠየኩ፡፡
ፍተሻውን ሳስበው ከበድ ያለ እንደሚሆን በመገመት ብቻ በሃሳቤ ብዙ ርቀት ተጓዝኩ፡፡ ያ ሁሉ ፍተሻ፣ ያ ሁሉ ‹‹የኮብራ›› መኪና ጋጋታ የሐሳብ የተፈጠረ የሆሊውድ ፊልም ጋጋት ነበር……..
እነ ዛ መጽሐፍት ግን ዋጋ አስከፍለውኛል ያልኩት፤ የገዛሁበትን ዋጋ ሳሰላስል ስለነበር ነው፡፡ ከአንድ ባለ አምስት ኮከብ አሊያም አራት ኮከብ ሆቴል ከማደር እነዚህን መሰል መጽሐፍት መግዛት አይሻልም ትላላችሁ…???¡¡¡
የውቢቷ ባህር ዳር “አዳር እና ውሎዬ” ግሩም ነበር፡፡ ዘመዴ ሁለት ልጆች አሏት አቤል እና ዳዊት ይባላሉ፡፡ /ስማቸው ለዚህ ጽፍ ሲባል የተየረ/
ዳዊት የ3 ዓመት ሕጻን ሲሆን፤ አቤል ደግሞ የ3ኛ ክፍል ህጻን ነው፡፡ እንዴት የሚያማምሩ ህጻናት መሰሏችሁ!!
ዳዊት ከዚህ በፊት አያውቀኝም፡፡ ስሜ በር ላይ ሲመዘገብ ብቻ ግን ሰምቷል፡፡ እቤት ከገባሁ በኋላ ሙሉ ስሜን ሲጠራው ተደነቅሁ፡፡
“ማን ነገረህ?” ስለው
“ክ..ክ…ድም ሰምቼ ነዋ!” አለኝ፡፡ እቅፍ አድርጌ ሳምኩት፡፡
እግሬን ስታጠብ ተከትሎኝ መታጠቢያ ቤት ገባ፡፡ “ሻሙና ላ..ንጣልህ” ብሎኝ “አዎ…” ከማለቴ በፊት ሮጦ ሄዶ ሳሙና አመጣልኝ፡፡
ወደጅ አግኝቷል፡፡
“ማነው ስምህ አልኩት…?”
`ዳ..ዳ..ዊት….
“ስንተኛ ክፍል ነህ?”
“አምሽት…!” /ሃሃ እድሜው 3 ክፍሉ አምስት!!/
ገና ጡጦውን እኮ አልጣለም፡፡ ግን አምስተኛ ክፍል ነው፡፡
“የት ነው የምትማረው- ጠየኩት፡፡”
“አካዳሚ////”
“የት አካዳሚ” ጠየኩት፡፡ “አካዳሚ ነዋ አ..አታውቀውም እንዴ..” ጠየቀኝ መልሶ…
//ባሕር ዳር አካዳሚ ታዋቂ ት/ቤት ነው፡፡ የእጅጋየሁ ሽባባው እህት የት/ቤቱ ባለቤት እንደሆነች ከዚህ በፊትም አውቅ ነበር፡፡
ጎረቤቱ ተሰብስቦ ቡና እየተጠጣ፣ በቆሎ እየተጠበሰ እኔም አንጠልጥያት የሄድኳት ደረቅ ብስኩት እየተጎረደመች/ በጣም አስቸጋሪ ነበር/ ስለ ት/ቤቶች ይወራ ነበር፡፡
“ባህር ዳር አካዳሚ እንደ ድሮው አይደለችም” በጣም ተቀዛቅዟል እየተባባሉ ሲያወሩ እሰማ ነበር፡፡
የዳዊት ታላቅ ወንድም ወደ ኔ መጣ፡፡ የቴሌቭዚኑን ሪሞት ኮንትሮል ይዞ፡፡
ቀኑን በሙሉ ቲቪ ላይ አፍጥጦ እንደሚውል አባቱ ነገረኝ፡፡ ያው ክረምት ስለሆነ ቤት ውስጥ ብቻውን ሲውል ይሕንን ‹‹የአረብ ዲሽ›› ይኮመኩማል፡፡
አቤል ሪሞቱን ሰጠኝ፡፡ ቀኑ ሐሙስ ስለሆነ ‹‹ኢ.ቢ.ኤስ›› ላይ የምከታተለው / የነ Habtamu Seyoum ‹‹የብራና ልጆች›› የተሰኘ ዝግጅት እንዳለ ነግሬው ሪሞቱን ተቀብሎ ቀየረልኝ፡፡
አብረን ተመለከትን፡፡ በጣም ወደዱት፡፡ ከዚህ በፊት አይተውት እንደማያውቁ ነገሩኝ፡፡ ከጀመረ ብዙም እንዳልቆየ እና ሁልጊዜ ሐሙስ ሐሙስ ከ2 ሰዓት ጀምሮ እንዲከታተሉ አስተዋውቄያቸው ወደ ሌላኛው ወሬ እና የቴሌቪዥን ዝግጅት ተሸጋገርን፡፡
አቤል የት ነው የምትማረው ብዬ ጠየኩት፡፡
“ኃይሌ” አለኝ፡፡ ----  እንዴት ነው ት/ቤቱ አልኩት፡፡ /የኃይሌ ገ.ስላሴ ት/ቤት ነው/
አቤል ለመመለስ ሲያመነታ አባቱ መለሰልኝ፡፡
“ባክህ እንደ ስሙ እና እንደሚጠበቀው አይደለም” ሲል መለሰልኝ አባት፡፤
“ምነው አልኩት…?”
“ያው ኃይሌ ሲጀመር በዓመት አንዴ ነው ብቅ ሚለው፡፡ ወላጅ ያለበትን ቅሬታ ሲያናግረውም”  ብሎ ጠለ፡-
“ዌል እንግዲህ ትምህርት ቤቱ የሁላችንም ነው.. በጋራ ተረባርበን ነው የምንገነባው… ችግሩቹንም የምንፈታው…..” ከማለት ውጭ ሌላ መፍትኄ ሲያመጣ አላየንም ብለው ስሞታቸውን ነገሩኝ፡፡ / ከመስማት ውጭ ምን እናደርጋለን- አንደንዴ የምሳማውን የምጽፈው ቢያንስ የሰውን ድምጽ ያስተጋባሁ አየመሰለኝ ነው፡፡/
ቀጠለ ወሪያችን፡፡ አንዱን አንዱን ስናወራ፡፡ እየመሸ መጣ፡፡ አቤል እና ዳዊት ዛሬ እንቅልፍ የላቸውም፡፡ አዲስ እንግዳ መጥቷልና፡፡
‹‹ጆሲ ኢን ዘሐውስ ሾ›› ጀመረ፡፡/ለምን በእንግሊዝኛ እንደሚጠራ አልገባኝም/፡፡
የዛሬው የትዕይንቱ ተጋባዥ እንግዳ ልጅ ያሬድ ነው፡፡
ሁላችንም አብረን ተከታተልነው፡፡ አቤል እና ዳዊትን ሳናያቸው አምልጠውን ወደ ክፍላቸው ሄደዋል፡፡ አቤል የልጅ ያሬድን ‹‹ስታይል›› ነው የምከተል ብሎ ጠጉሩነ ላይ የቦሎውን ጭራ ነስንሶ መጣ
ዳዊት ደግሞ የጆሲን ‹‹ስታይል›› አስመስሎ ጠጉሩን እንደ አውራ ዶሮ ቆብ ሰበጥሮ መጣ፡፡ የጆሲ ኢን ዘ ሀውስ ሾ ለሕጻናት የሚፈድ ነው… በተለይ የልጅ ያሬድ እንግድነት ህጣናት የማይደርሱበት ቦታ ተብሎ መለጠፍ ነበረበት… ዘንዶ ጋር ይተኛ ነበር… ጫካ ውስጥ ይኖር ነበርና… እኔም ፈርቼ ነበርና…!
ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚተላለፉ መሰል ዝግጅቶች የሚደርሰውን ተጽዕኖ ማን ነው ኃላፊነቱን የሚወስደው? ቤተሰብ? የጥበብ ሰዎች? መንግስት?......
ከመጣነው መንገድ ይልቅ የምንጓዘው ያሳስበኛል… እናንተንስ?
መሸ… ተኛን… ብለሜ ለ24 ሰዓታት ከአብርሃ ደስታ ጋር እንደታገትኩ ተመለከትኩ… ያ ሁሉ ህልም ነበር፡፡ ሃሰቡን ተጋራሁት!! የማለዳ ወፍ በጥዋት ቀሰከሰችን//// የማለዳ ወፍ!!
ቁርስ ቆረስን… ለመዋያ የሚያገለግለኝን ቁልፍ ተረከብኩ… ዋው….!!!!! ባህር ዳርን በብስክሌት---- እንዴት ታምራለች!!!
ብዙ መንገድ ተጓዝኩ…. ከመጣሁት ይልቅ የምጓዘው ረዥሙ እንደሆነ  እየተሰማኝ ነው… እናንተስ?
Bahir Dar









Jul 14, 2014

የ2014 የእግር ኳስ ዐለም ዋንጫ

የ2014 የእግር ኳስ ዐለም ዋንጫ

ድሮም የጠላነው ይሕንን ነው፡፡ በኳስ ስም፣ በመዝናኛ ስም፣ በአገር “አንድነት” “ነጻነት” እና “ሰላም” ስም የሚሰራውን ሴራ! የ2014ቱ አለም ዋንጫ ሲጀመር የታዩትን ምስጢራዊ ምልክቶች፣ የብራዚል ህዝብ እንባ እና አለም ላይ እተካኄደ ላለው ኢ-ፍትሃዊነት ምላሽ ሳይሰጥ አለምን አንድ አደርጋለሁ የሚለው አስተሳሰብ ሁልጊዜም አይዋጥልኝም!
ፍልስጤማውያን ህጻናት ጭንቅላታቸው ኳስ ባነሰ ዋጋ ሲነዳደል… አፍሪካውያን ፖለቲከኞች እየሰቃዩ… ይባስ ብሎ በሀይማኖት ላይ ሲዘበት ስናይ ይሕንን ስርዓት እነድንጻረር እና እንድንቃወም ያስገድደናል!!
ኳስን አልጻረርም፣ ሰው አልፈጠረውም እና፡፡ እግር አይን እጅ መሮጥ መቀናጀትን ሰው አልፈጠራቸውም እና! ነገር ግን በስመ ኳስ እየተላለፈ የሚገኘውን የምስጢራዊ ቡድናት ህገ-ወጥነት እና ሴራ አጥብቄ እቃወማለሁ! የዚህ ማሳያም ምሳሌ እነዚህ ምስሎች ናቸው…


2
3

Jul 13, 2014

አበበ ተካን ስንመለከት ምን ተሰማን?

አበበ ተካን ስንመለከት ምን ተሰማን? የፖለቲካ አስረኞችን ስንሰማ? 
‹‹‹‹‹‹‹ተስፋ በላይነህ›››››››


እንደ ኢትትዮጵያ ያለ አሳዛኝ አገር አለ ለማለት ያስቸግራል፡፡ እርግጥ ነው አገር የተባሉት ሁሉ ችግርን እንደተሸከሙ እናያለን፡፡ ፍልስጤምን አሻግረን እናያለን፡፡ የአገር ስያሜ ባይኖር በምን ስም ይሰቃዩ ነበር? የሰው ልጅ በአገር ጥላ ስር ሲጠለለል ከዝናብ፣ ከዶፉ- ከሐሩ ከእሳቱ- ከረሃብ፣ ስደቱ- ከጦርነት፣ እልቂቱ ሊከለል እና ሊጠበቅ እንጂ በአገር ስም ሲዋረድ እና ሐሞቱም ሲፈስ ደሙ ሲፈስ የሚታይበት ምክንያት ምንድን ነው?

ለመሆኑ አገር ማለት ምንድን ነው? አገር ለሰው ልጅ ሥለምን የእልቂት እና የስደት- እንዲሁም የምድር ጣር መገለጫ መንስዔያት ሊሆን ቻለ? ለምን ? አገር የመሬት የህዝብ እና የመንግስት ስብጥር/ሕብረት መገለጫ ሆኖ ሳለ መሬት እና ህዝብ የት ሄደው ነው መንግስት በብቸኝነት አገርን የሚመራው? እስከመቼስ እንዲህ ይኖራል? ለጠያቂዎች ያልሆነ መሬት እና ጠያቂ የሌለበት ህዝብ ሲገዙ መኖርን ማን ፈቀደው? /ሲገዙ- ጠበቅ ይበል!/

ሰሞኑን ታሰሩ የተባሉ ግለሰቦችን በየማህበራዊ ገጾች እና በመገናኛ ብዙሃን ስንሰማ ቆይተናል፡፡ ነገም ማን ታስሮ እንደሚጠብቀን አናውቅም..! ታሰሩ የሚባሉትንም ግለሰቦች የታሰሩበትን ምክንያትም አናውቅም…! ምን እንደሚሻለንም አናውቅም፡፡ አመት አመትን ሲሸጋገር ይዘን የምንሻገረው ነጻነትን፣ ፍትህን እና አንድነትን ወይንም ሰላምን አይደለም፡፡ አሊያም ከማንኛውም አይነት አገራዊ ክስተቶች መራቅ የግድ ሊሆንብ ነው ማለት ነው! 

አበበ ተካን ስንመለከት ምን ተሰማን-? የኑሮው ውጣወረዱ፣ የግል ስብዕናው ወይንም ፍልስፍናው፣ በቀልድ እያዋዛ የሚያቀርበው ማንነቱ ምን ተሰማን? እኔ ግን አገር አልባ ማንነታችንማንነት አልባ ስብዕናችንአገር አልባ ተስፋችንስቃይ እና ናፍቆት ከሁሉም በበለጠ ይህች አገር እንዲህ እየሆነች ማዬት ህመም ነውኢትዮጵያዊነቱን ተነፍጎ ከአገር አገር መንቀሳቀስ እንዳይችል ተደርጎ ከእስር በማይሻል ሕይወት የሚኖር ሰው አገሩ መምጣት ያልቻለበት ምክንያት የግል ጣጣው ነው ወይንስ የአገር ጣጣ?

ማን ነው እንዲህ እንድንሆን የፈረደብን? አገር ውስጥ ያለነው ስለ አገር ሙሉነት ስሜት እንዳይሰማን- ሙሉ በሙሉ እንዳንሰማ- እንዳንሳተፍ- ታሪክ ባሕል እና ፖለቲካን እንድንሸሽ እያደረገን ያለው ማን ነው…?

ህሊናን በብልኮ እንድንጋርድ፣ ዛሬን ለጥጠን እንድንኖር፣ ነገን ሳናስተውል ኑሮን እየገፋን እንድንኖር ያደረገን ማን ነው? መብላት መጠጣት ማውራት መተኛት የሕይወት ምስጢር አድርጎ አቡክቶ የሰራን ማን ነው? ምንድን ነው? ለምንድንስ ነው?


አገሬ ኢትዮያን እንዲህ እንድትሆን ያደረጋት ማን ነው? ወደየት እናዘግማለን? የት ነን? ምንድን ነን?