አዲሲቷ ኢየሩሳሌም
በምድር አሜኬላ፤
በአለም ከንቱ ተድላ፡-
በባቢሎን አጥር፤
ካመፃዋ ቅጥር ፡-
ከገባሽ መንፈሴ፤
ካለሽ አንቺ ነፍሴ፡-
ውጪ ከመንደሯ፤
ተለይ ከምግባሯ ።
αΩ αΩ αΩ αΩ αΩ
መጣች ተሸልማ፤
ወረደች ሙሽራ በቀደመው ክብሯ።
እንባዬን ልታብስ ፣
ኀዘኔን ጩኸቴን ስቃዬን ልታድስ፡-
«አልፋና ኦሜጋ» የምንጭ ውሃ ሲፈስ።
ራዕዬ ዮሐንስ ፳፩፡
፩-፯ (21፡1-7)
No comments:
Post a Comment