Jul 25, 2013

ስንት ዳዊቶች በጎልያዶች ወድቀዋል…?






ስንት ኢትዮጵያኖች ለጥበብ ተጠምተዋል…?
ስንት ዳዊቶች በጎልያዶች ወድቀዋል…?
በተስፋ በላይነህ
ይህ የአንድ ኢትዮጵያዊ ታሪክ ነው፡፡ የአንድ ኢትዮጵያዊ እንጅ የኢትዮጵያ ታሪክ ግን አይደለም፡፡ ኢትዮጵያ ታሪክ አላት፤ ይህ ልጅ ግን ታሪክ የለውም፡፡ ከባለታሪክ ሀገር “አልቦ ታሪክ” ïነን ስንገኝ ያሣዝናል፡፡ ኢትዮጵያ የታሪክ መዘክር ናት፡፡ ኢትዮጵያኖች ግን ታሪክ አልባ እየïኑ ነው፡፡ ኢትዮጵያኖች ታሪክ አልባ ከïኑ ኢትዮጵያስ ታሪካዊነቷ ምኑ ላይ ነው? ህዝብ ታሪክ አልባ ሲïን ሀገር ምን ትïን? ይህ ግን የአንድ “ታሪክ አልባ ኢትዮጵያዊ ታሪክ” ነው፡፡ በዚህች ሀገር ጥበብ በብርቱ ትፈለግ ነበር፡፡ ጥበብን የሻተች ንግስት ወደ ጠቢበኛው ለምስክርነት የተዘከረች ሀገር ነች፡፡ ለጥበብም ለመፍረድ የምትነሳ! ህዝቦቿ ግን በጥበብ መሪነት ሲጓዙ አልታዩም፡፡ ሲገዙም አልተሠሙም! ህዝቦቿ ግን ጥበብ አልባ፣ ታሪክ አልባ፣ ሀገር ለልባ ሲïኑ እየታዘብን ነው…. ዳዊት ይባላል ባለታሪኩ፡፡
የአስረኛ ክፍል ትምህርቱን ጨርሶ ወደሚቀጥለው የትምህርት ደረጃ ማለፍ አትችልም ተባለ፡፡ ቤተሰቦቹ ብዙ ይጠብቁ ነበር፡፡ ሕይወት አንድ ቀጥተኛ መንገድ አለመïኗን ሳያስተምሩ ለአንድ ትልቅ ቦታ ይመኙታል፡፡ ከህፃንነት ጀምሮ በርካታ መጽሐፍትን አስነብበውታል፡፡ ከ “ኬጂ” ጀምሮ የሚያቀላጥፈው እንግሊዘኛ ቋንቋ አሁን ከፍተኛ ተናጋሪ አድርጎታል፡፡ ሶስት ተጨማሪ ቋንቋዎችን ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ አሉ የተባሉ መጽሐፍትን በቤቱ አሟልቷል፡፡ ያነባል…. ሙዚቃ ያደምጣል… ፊልም የቀረው የለም… አሥረኛ ክፍልን በእንደዚህ ጉዞ ፈጽሟል፡፡ አባቱ “የፖለቲከኛ እስረኛ” ናቸው፡፡
ህይወት “ማለፍና መውደቅ” መïኗን ባነበባቸው፣ በተመለከታቸው እና ባደመጣቸው መጽሐፍት ፊልሞች እና ዘፈኖች ተምሯል፡፡ ነገር ግን- ነገር ግን ለአስረኛ ክፍል መውደቅ መከታ አልïኑለትም፡፡ የባስ የወደፊት ህይወቱን አጨለሙበት፡፡ በየሙዚቃው በየፊልሙ የሚያያቸውን የአልባሣት፣ የመጓጓዣ፣ የመኖሪያ እና የመዋብያ ንዋያትን የሚያገኘው ተምሮ ጨርሶ በሚያገኘው “ገንዘብ” እንደïነ ተነግሮታል፡፡ ካልተማረ እነኚህን ኹሉ የግሉ ማድረግ አይቻለውም፡፡ ቆነጃጅት ሴቶችን ማማለል የሚቻለው እነኚህ ሲሟሉ እንደïነ ተማምኗል፡፡ አሁን ግን እነኚህ ነገሮች የሉም ህይወትም የለችም!
ለሣምንታት ከቤተሰቦቹ ተገልሎ ቆይቷል፡፡ ማንንም ማነጋገር አይፈልግም፡፡ ከጆሮው በሠካት ማፅናኛ ብቻ ቀኑን በሙሉ ይገፋል፡፡ ይጮኻል ዘፈኑ… ይጮሃሉ ዘፈኖቹ… ይጮኻል መሣሪያው… መጽናኛው “ሙዚቃ” ብቻ ነበር፡፡
ከህፃንነት ጀምሮ አብራው ያልተለየች ልጅ አለች፡፡ ዘፈኑ በሙሉ ለእርሷ ነው፡፡ ህይወት በሙሉ ለእርሷ ነው፡፡ ሲፈልግ ያሞግሳታል… ሲያሻው ያብጠለጥላታል… ካሠኘው ያመልካታል… ከመጣበትም ይቃወማታል፡፡ ይኽ ሁሉ የሚነገረው በዘፈኑ ነው፡፡ ዘፈኑ ቀኑን በሙሉ ከጆሮው አይለይም…! ዘፈኑ “ሮክ” ነው፡፡
በደመነፍሥ ይራመዳል፡፡ መሄጃ የለውም ግን ይጓዛል፡፡ ሃሣብ የለውም ግን ይጨነቃል፡፡ ሰሚ የለውም ግን ያወራል…! ምናልባት ስሜቱን ተረድታ፤ በቀዘቀዘው ማንነቱ ውስጥ ገብታ የምታሞቀው አብሮ አደግ “ጓደኛው” ሚልካ ትኾናለች፡፡ የሚያደምጠው ሙዚቃ ናፍቆቱን ቀስቀሰበት፡፡ እንደውም ወደርሷ እንዲሄድ ገፋፋው… ጉዞ ወደ ሚልካ፡፡
I miss you miss you. Don’t waste your time on me you already the voice inside my head. I miss you. Miss you….እያለ ይዘፍናል፡፡ ሜልኮል በአእምሮው ውስጥ ትጮኽበታለች፡፡ ናፍቆት “በልቡ” ይወዛወዛል፡፡ ሄደ ማየት አለበት፡፡
ዝናቡ ከዛሬ ውጪ የሚዘንብ አይመስልም፡፡ ሠማይ ተከፍቶ የሚዘጋም አይመስልም፡፡ ይዘንባል! ዳዊት ወደ ሚልኮል እየሄደ ነው፡፡ ዝናቡን በትከሻው ተሸክሞታል፡፡ ቤታቸው ፊት ለፊት ደረሰ፡፡ ባለፎቅ መኖሪያ ቤት ውስጥ ፊት ለፊት የሚያየው በመስኮት ሜልኮልን ነበር፡፡ ዝናቡ አስገርሟት “በሣቅ” ትመለከታለች፡፡ ያዘነው ዳዊት ስልኩን አውጥቶ መደወል ጀመረ… አነሣችው…
ሄሎ ዴቭ…
ሄሎ…
እንዴት ነህ?
አለሁ…
በጣም ጠፋህ በሰላም ነው?
አለሁ አንቺስ ምነው አልደወልሽም? እደውልልሃለሁ… ሣይጨርስ ተቀበለችው
አይ ዴቭ ሰሞኑን እኮ ክፍለ ሃገር ሄጄ አልተመለስኩም፡፡ ዳዲ ዘመድ ምናምን እያለ የሚጨርሥም አይደለም፡፡ ስንመለሥ አገኝሃለሁ….
ማመን አልፈለገም፡፡ መጠየቅም አልፈለገም፡፡ ማረጋገጥ ግን አለበት….
ታዲያ አሁን ቤት አይደለሽም? አለ በፍርሃት አንደበት…
አዎ! ክፍለ ሃገር ከሄድኩ ቆየሁ፡፡ በማለት የመስኮቷን ነጭ መጋረጃ ፈታች፡፡ ነጭ መጋረጃው ክፍለ ሃገር ሸኛት… ነጭ መጋረጃው ዳዊትን ጥቁር አለበሠው፡፡ ዝናቡ በመብረቅ ታጀበ፡፡ ዳዊት እንደ ጨው ሟሟ፡፡ የግቢውን ረዥም አጥር ኮረንቲ መጠጣት አሰኘው…ዝናቡም ዳዊትን አጥቦት ይዞት ጎረፈ፡፡ Jump to fire የሚል ዘፈን ቀጠለ… (ሰባት ዓመት…..)
ከሰባት ዓመት በኋላ ዳዊት አልተመለሠም፡፡ የሚዘልበት እሣት አላገኘም ልቡ ግን እሣት ይተፋል፡፡ ሲጋራ… ሬት ሲጠጣ ይውላል… ቅጠሉ መምረሩ እንደጣፋጭ ïነለት፡፡ 7 ዓመት መቃም… ሠባት አመት መጨስ… ከ97 ጀምሮ!
“ታላቁ መሪ” ሞቱ የሚል ወሬ ይሠማል፡፡ ዳዊት እንኳንሥ መሪውን ሱሪውን በስርዓት ለይቶ አያውቅው… አያወልቅምም! ቀይ ደም ቀርቶ አረንጓዴ ደም “ከልብ ስሩ” ይረጫል! ፀጉሩ አያቱ ከሚፈትሉት ፈትል በይበልጥ ተፍተልትሏል፡፡ ጡንቻው እናቱ ከምትለብሰው ነጠላ በይበልጥ ተሸብሽቧል… የብብቱ ጠጉር መነኩሴን ያስመንናል… ታጋይን ይሸሽጋል… አርበኛን ያስኮበልላል… ለዳዊት ፀሃይ ጠልቃ አልወጣችም… ጨረቃ ሞልታ አልተገመሠችም… ከዋክብትም ረግፈዋል… “ነጋ ጠባ ሰኞ አመት ሙሉ ሰኔ…!” ዳዊት ተፈርዶበታል!(ፊያሜታ)
ዳዊት ኢትዮጵያዊ ነው! ስንት ዳዊቶች ሣይኖሩ ሞተዋል? ስንት ኢትዮጵያኖች ሣያድጉ ረግፈዋል…? ስንት ኢትዮጵያኖች በጩኸት ደንዝዘዋል? ስንት ኢትዮጵያኖች ተሸሽገው አድፍጠዋል..? ስንት ድንጋዮችስ ተጠርበው፣ ተውበው ህንፃ ኾነዋል? ስንት ዳዊቶች ተውበው፣ ተጠርበው፣ ተቀብረዋል…? ስንት “ኮብሎች” ተፈልጠው መንገድ ኾነዋል…?  ስንት ጉብሎች ተጠልፈው መንገዱ ጠፍቷቸዋል…? ስንት ጀግኖች…? ስንት ጠቢባኖች ተሠደዋል…? ስንት ታሪክ አዋቂዎች በመንፈስ ተኮላሽተዋል…? ስንት እውነት ፈላጊዎች  ታስረዋል…? ስንት ነፍሳት ተነጥቀዋል…? ስንት “ሜልኮሎች” በዳዊቶች ተሣልቀዋል….? ስንት ዳዊቶች በጎልያዶች ወድቀዋል…? ስንት ኢትዮጵያኖች ለጥበብ ተጠምተዋል…? ኢትዮጵያ ሆይ ስንት…? ፡-(
www.tesfabelaynehh.blogspot.com
ቸሩ ቸር ያቆዬን!

No comments: